በኩባንያችን የደም ልገሳ ፕሮግራም ተካሄደ።

የኩባንያችን አመራሮችና ሰራተኞች በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ላይ ለሚገኙ የመከላከያ  ሰራዊት፤ ልዩ ሃይል እና ፋኖ ቀደም ብሎ የተጀመረውን የገንዘብ ድጋፍ በአዲስ መልክ በማጠናከር የአንድ ወር ሙሉ ደመዎዝ ከ1.6 ሚልዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጋቸው ይታዎቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያችን የ2.8 ሚልዮን ብር የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ እና ለህልውና ዘመቻው አገልግሎት የተለያዩ ቀላልና ከባድ ተሸከርካሪዎች እንዲሁም የሎጅስቲክስ ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን ሚና እየተወጣ ይገኛል፡፡

በዛሬው ዕለትም ( ነሃሴ-19/2013 ዓ.ም) በኩባንያችን ቅጥር ግቢ በመገኘት የደም ልገሳ ፕሮግራም በማካሄድ የዜግነት ግዴታችውን በመወጣት ለህልውና ዘመቻው አጋርነታቸን አሳይተዋል፡፡

May be an image of 2 people and people sitting


Leave a Reply

This website uses cookies and asks your personal data to enhance your browsing experience. We are committed to protecting your privacy and ensuring your data is handled in compliance with the General Data Protection Regulation (GDPR).