በ2ኛው ዙር የፌዴራል ግብር ከፋዮች ሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ኩባንያችን ተሸላሚ ሆነ።

የገቢዎች ሚኒሰቴር የታማኝ ግብር ከፋዮች ሽልማትና ዕውቅና ሰጥቷል።ተሸላሚዎቹ ከሀገር ውስጥ ታክስና ከጉምሩክ ቅርጫፎች የተመረጡ ናቸው፡፡

በዚህ በቤተመንግስት በተዘጋጀው በዚህ 2ኛው ዙር የፌዴራል ግብር ከፋዮች ሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ኩባንያችን አንዱ በመሆን የብር ዋንጫ ተሸላሚ ሁኗል። ኩባንያችን ባለፈው ዓመት በተካሄደው የመጀመሪያው ዙር የምስጉን ግብር ከፋዮች ሃገር አቀፍ እውቅና አሰጣጥ ፕሮግራም ላይም ተሸላሚ መሆኑ ይታወሳል።

ታማኝ ግብር ከፋይ በመሆናችን ላገኘነው ለዚህ ሽልማት ጉልህ ሚና የነበራችሁ የኩባንያችን ሰራተኞቻችንና አመራሮች እንዲሁም ባለድርሻ አካላትን ለማመስገን እንወዳለን። ለአገራችን የሚጠበቅብንን አስተዋጽዖ ለማበርከት በቀጣይም ተግተን እንሰራለን።



Leave a Reply

This website uses cookies and asks your personal data to enhance your browsing experience. We are committed to protecting your privacy and ensuring your data is handled in compliance with the General Data Protection Regulation (GDPR).