የሐዘን መግለጫ

የኩባንያችን ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ዘመኑ ዋለልኝ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ስንገልጽ በተሰበረ ልብ ውስጥ ሆነን ነው።
አቶ ዘመኑ ዋለልኝ ከአባታቸው ከቄስ ዋለልኝ ቢሻው እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ላቀች አሰጌ ጥር 5 ቀን 1968 ዓ/ም በምዕራብ ጎጃም ዞን ጃቢ ጥህናን ወረዳ ተወለዱ። ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ባለመቻሉ በተወለዱ በ44 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። አቶ ዘመኑ ዋለልኝ ባለ ትዳርና የአንድ ሴት ልጅ አባት ነበሩ።

በኩባንያችን ዋና ሥራ አስኪያጅ ህልፈተ ህይወት የተሰማንን መሪር ሐዘን እየገለጽን ለመላ የኩባንያችን ሰራተኞች፣ ለቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።



Leave a Reply

This website uses cookies and asks your personal data to enhance your browsing experience. We are committed to protecting your privacy and ensuring your data is handled in compliance with the General Data Protection Regulation (GDPR).