ጉማራ ወንዝ ላይ የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ እየተሠራ ነው።

በደቡብ ጎንደር ዞን ደራና ፎገራ ወረዳዎች ክረምት በገባ ቁጥር ተደጋጋሚ የጎርፍ አደጋ የሚከሰትባቸው አካባቢዎች ናቸው፡፡ የጉማራ ወንዝ መሙላት ለአደጋው መከሰት አንድ ምክንያት መሆኑ ይታወቃል። በተደጋጋሚ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ቀጥተኛ ተጎጂዎች ሆነዋል፤ ሰብል ወድሟል፤ የቤት እንስሳት ሞተዋል፤ ንብረት ለውድመት ተጋልጧል።በያዝነው ዓምት ይህን አደጋ ለመቀነስ ጉማራ ወንዝ ላይ ኩባንያችን የጎርፍ መከላከያ በመስራት ላይ ይገኛል። በዚህም የኩባንያችን ማሽኖች ገብተው እየሰሩ ይገኛሉ፡፡



Leave a Reply

This website uses cookies and asks your personal data to enhance your browsing experience. We are committed to protecting your privacy and ensuring your data is handled in compliance with the General Data Protection Regulation (GDPR).